Wednesday, 17 May 2017



ተዘዋዋሪ   ፈንዱ  ለታለመለት..
መንግስት የኢትዮጵያ ወጣቶች የዕድገት እና የልማት ፖኬጅ ቀርፆ የተዘዋዋሪ ፈንድ በመመደብ ወጣቶችን በጥቃንንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በማደራጀት ወደ ሥራ እንዲገቡ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
በፌዴራል ደረጃ ለወጣቱ ሥራ እድል ፈጠራ 1ዐሚ ብር ተዘዋዋሪ ፈንድ ተመድቦ ለሁሉም ክልሎችና ወረዳዎች ድልድል የተጠናቀቀ ሲሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ማለትም የሥራ አጥ ወጣቶች ምልመላና ምዝገባ፣ ግንዛቤ ፈጠራ እና የማማደራጀት ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቀዋል፡፡
በዚህ የወጣቶች የዕድገትና የልማት ፓኬጅ  በክልላችን በሚገኙ ከተማ አስተዳደሮች፣ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች የሚገኙ እና ነዋሪ የሆኑ ወጣቶች ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡ እነዚህ ወጣቶች የኢትዮትያ  ዜግነት ያላቸውና ከ18-34 ዕድሜ  ባለው ክልል የሚገኙ ይሆናሉ፡፡
ተዘዋዋሪ ፈንዱ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚተላለፍ ሲሆን ባንኩም ለሥራ ዕድል ፈጠራ ለሚታወቀው ለአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በብድር መልክ ያቀርባል፡፡ አበቁተም በክልላችን በሚገኝበት ከተማ  አስተዳደሮች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለተደራጁ ወጣቶች ይህን ገንዘብ በብድር ያስተዳድራል፡፡ ይህንን የወጣቶች ተዘዋዋሪ ገንዘብ ለታለመለት አላማ በውጤታማነት ለመጠቀም ግልፅ የአሠራር መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
ወጣት ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ብድር የሚሰጥበት አሠራር፡-
- በኢንተርፕራይዝ ለመደራጀት የሚመለመለው ወጣት በቀበሌው በአንድ ማዕከል የሥራ አጥ መመዝገቢያ መዝገብ ላይ የተመዘገበ መሆን
- የሚመለመለው ወጣት የአዕምሮ ህመም የሌለበት እንዲሁም የደባል ሱስ ተጠቂ ያልሆነ፣ በመጥፎ ሥነ-ምግባር  የማይታወቅ ፣ የመስራት አቅምና ችሎታ ያለው
- የተመለመሉ ወጣቶች የንግድ ሥራ አመራር /የኢንተርፕረነርሽፕ/ ሥልጠና መውሰድ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በሽርክና ማህበር የተደራጁ እና ቢያንስ 5 አንከሳቃሾች ያላቸው መሆን ይኖርባቸል፡፡
- ወጣቶች ሲደራጁ በፍላጐት ላይ የተመሠረተ ሆኖ በተቻለ መጠን የሚተዋወቁና በአንድ አካባቢ የማኖሩ ቢሆኑ ይመረጣል
- የሚደራጁ ወጣቶች ከዚህ ቀደም ከፋይናንስ ተቋማት የተወሰደና  እና የተበላሸ ውዝፍ እዳ የሌለባቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ኢንተርፕራይዞቹ የብድሩ ተጠቃሚ ለመሆን ለሥራውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ ቢያንስ 1% ከሚወስዱት የተቋሙ ቅርንጫፍ መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ለሚወስዱት ብድር የአንድነትና የነጠላ ዋስትና መፈረም ይኖርባቸዋል ለብድሩ ውጤታማ ተጠቃሚነት የቤተሰብ ትስስር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በኢንተርፕራይዙ የሚደራጁ ወጣቶች ሲመለመሉ መስፈርቱን ለሚያሟሉ  ሴቶች ቅድሚያ ይሰጣል፡፡
- የሥራ መስኩ ምርጫው ሙሉ በሙሉ በኢንተርፕራይዞቹና በአባሎቻቸው ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ይሆናል፡፡

የኢንተርፕራይዞች የሥራ መስክ
- ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ገቢ ሊየስገኙ በሚያስችሉ ማናቸውም አይነት የሥራ መስኮች ሊሠማሩ ቢችሉም በክልላችን ተጨባጭ ሁኔታ እድገት ተኮር የሥራ ዘርፎች እና የተመረጡ የአገልግሎት የሥራ ዘርፎች ይሆናሉ፡፡
-ፍላጐታቸውን ማዕከል አድርገው በመረጡት የሥራ መስክ ላይ አዋጭነት ያለው የሥራ ዕቅድ  (Business plan)  ማዘጋጀተ ይኖርባቸዋል፡፡
                  የብድር መጠን
- ኢንተርፕራይዞች የሚወስዱት የብድር መጠን እንደሚሠማሩበት የሥራ ዘርፍ  እና ደረጃ የሚስያማ ቢሆንም ለአንድ ኢንተርፕራይዝ   ሊፈቀድ የሚችለው ከፍተኛው የብድር መጠን ከብር አንድ ሚሊዮን  (1,000,000) eJsB vsjUE!!
      
            የብድር ወለድ
· ጥቃቅን  ኢንተርፕራይዞች በሚወስዱት ብድር ላይ 8 በመቶ አመታዊ ወለድ ይከፍላሉ
· ጤናማ ባልሆኑ ብድሮች ላይ የተጨማሪ 1.5 በመቶ የቅጣት ወለድ ያስከፍላል፡፡


       የብድር መክፈያ ጊዜ
- የኢንተርፕራይዞቹ የሚወስዱት ብድር የመክፈያ ጊዜ እንደተሠማሩበት የሥራ መስክ እና እንደወሰዱት የብድር መጠን ሊለያይ ይችላል፡፡
- በአብዛኛው በአማካይ የብድር መመለሻ ጊዜው 3 ዓመት የሚጠናቀቅ ሆኖ እንደአስፈላጊነቱ በተመረጠ ዘርፍ የብድር ክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜው እስከ 5 ዓመት ሊደርስ ይችላል፡፡
በአጠቃላይ ለኢንተርፕራይዞች ውጤታማ የሚማያደርገውን ተከታታይነት ያለው ድጋፍ በመስጠት የመመለሻ ጊዜው በአግባቡ ማስመለስ ይገባል፡፡
በአሁኑ ሰዓት የአዊ ብሔ/አስ///ኢን//በሥራ ካሉ /ቤቶች ጋር በመሆን 54 በላይ ሥራ ፈላጊዎችን መዝግቦ የማደራጀት ሥራዎች ተጠናቀዋል፡፡
በፌዴራል የተዘዋዋሪ ፈንድ የብሔረሰብ አስትዳደራችን ድርሻ  160 ሚሊዮን ብር ሲሆን ከዚህ በታች የወረዳዎች ድርሻ ድልድል እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

 የተዘዋዋሪፈንድበጀትድልድልበየወረዳደረጃ
ተራ
.
የወረዳውስም
የወጣትብዛት
የብርድርሻ /የወጣትቁጥር
*362,316 ብር/
2ዐዐ9 በጀትዓመትድርሻ
ወንድ
ሴት
ድምር
 1
አዊብሔረሰብአስተዳደርዞን





 2
እንጅባራከተማአስተዳደር”
12,356
12,273
24,629
8,923,48.76
4,461,74.38
 3
ዳንግላከተማአስተዳደር
8,512
11,788
2,3ዐዐ
7,355,14.8
3,677,57.4
 4
ቻግኒ
6,494
8542
15,036
544,778,338
272,389,169
 5
ባንጃ
13,638
16,61
3,239
1,956,73.52
5,478,36.76
 6
ጓጉሳሽኩዳድ
16,92
2,554
37,456
13,57,98.1
6,785,454.5
 7
አንከሻ
35,86
42,337
78,143
28,312,459.19
14,156,229.6
 8
ዚገም
15690
18824
34514
12,504,974.42
6,252,487.21
 9
ጓንጓ
2,349
24373
44,772
16,23,496.15
8,11,748.8
1
ጃዊ
26,519
27,190
55,709
20,184,262.04
10,092,131.02
11
ዳንግላወረዳ
21,361
25,122
46,483
16,841,534.63
8,420,767.32
12
ፋግታለኮማ
26,163
28859
5522
1993535.95
9,967,675.48

ድምር
25,79
236,463
442,253
16,235,337.9
8,117668.95
 DSC_0269DSC_1061











 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 በአዊ ብሔ/አስ/መኮ// መምሪያ

መንግስት ኢንፎርሜሽን የሥራ ሂደት የተዘጋጀ

ሚያዚያ  2009 .

 

· ' 0582271428
· 6 0582270037        * 64
· Fb. page Awi communication
   እንጅባራ 




No comments:

Post a Comment