ልማታዊ መንግስት ለቋንቋዎች ዕድገት!
ልማታዊ መንግስት ለዜጎች ካጎናፀፋቸው መብቶች አንዱና መሰረታዊ ጉዳይ የዜጎችን ሠባዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ማክበርና ማስከበር ነው፡፡ ይህም ሲባል ዜጎች የራሳቸውን ቋንቋና ባህል በማሳደግ በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ፣ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ እንዲሁም የራሳቸውን ባህል እንዲያሳድጉ ማድረግ ነው፡፡
ውድ አንባቢያን በዚህ ዓምድ ልማታዊ መንግስት ዜጎች አፍ መፍቻ ቋንቋቸውን እንዴት ማሳደግ እንዳለባቸው የወሰደቸው የህግ ማዕቀፉ የሰጣቸውን መብቶች ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ - መንግስት ካጎናፀፏቸው ሰብአዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ህገ - መንግስታዊ መብቶች አንዱ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የመናገር መብት ነው፡፡ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል በአፍ መፍቻ ቋንቋው የመናገር፣ የመፃፍ፣ ቋንቋውን የማሳደግ፣ባህሉን የመግለጽ፣ የማዳበርና የማስፋፋት እንዲሁም ታሪኩን የመግለጽ መብት አለው፡፡ ሆኖም ባለፉት ዘመናት ዜጎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የመናገር መብታቸው ተነፍጓቸው በማንነታቸው እንዲሸማቀቁ፣ በቋንቋቸውና በባህላዊ አኗኗር ዘይቤአቸው እንዳይኖሩ፣ ትውፊታቸውንና ወጋቸውን እንዳያለሙ በጨቋኝና አፋኝ ስርዓቶች ጫና ይደረግ እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ ይሁን እንጅ በዜጎች መራር ትግል እነዚያ የግፍ ዘመናት ድል ተደርገው ዛሬ ላይ ሁነን ስንቃኘው የአገራችን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ህዝቦች በህገ -መንግስቱ የተረጋገጠላቸውን መብት በመጠቀም 46 ቋንቋዎች የፅሁፍና የትምህርት ቋንቋ እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ ከዚህም መካከል 17 ቋንቋዎች በፊደል እስክሪፕት እና 29 በላቲን እስክሪፕት የሚጠቀሙ ናቸው፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተሰጠው ተግባርና ሀላፊነት አንፃር የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቋንቋዎች ስነ ቃሎች ትውፊቶች፣ኪነ-ጥበባዊ እውቀቶች ለአገልግሎት እንዲውሉ፣ የቋንቋና የጋራ ባህላዊ እሴቶች እንዲበለፅጉ፣መጤንና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች እንዲወገዱ፣ የህዝቦች አመለካከት ለማህበራዊ እድገት ለምተውና በልጽገው ለሀገራዊ ልማት እንዲውሉ ማድረግ ዋና ዋና ተግባራት ናቸው፡፡ ተግባራቱ እውን እንዲሆኑ በህብረተሰቡና በባለድርሻ አካላት ተሳትፎ በማጥናት፣ በልማትና በማስተዋወቅ እንዲሁም የአገሪቷን መልካም ገጽታ በመገንባት ዘላቂ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጥቅም እንዲሰጡ ተልዕኮ በመያዝ ያላለሳለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አገራችን ብዙሃነት ተቀብላ በእኩልነት እያስተናገደች ያለች ሀገር እንደመሆኗ ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት/ ዩኔስኮ/ ጋር ካደረገቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች አንዱ በቋንቋ ብዙሃነት ላይ የተደቀነውን ስጋት አብሮ በመስራት ለመቀነስ እንዲሁም የቋንቋ ልማት በሀገሪቱ እንዲረጋገጥ ከህብረተሰቡ ጋር ግንዛቤ የሚፈጥሩ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ - መንግስት በምዕራፍ 1 በአንቀጽ 5
/1-3/ ላይ ማናቸውም የኢትዮጲያ ቋንቋዎች በእኩልነት የመንግስት እውቅና ይኖራቸዋል፡፡ አማርኛ የፌዴራሉ መንግስት የስራ ቋንቋ ይሆናል፤ የፌዴሬሽኑ ም/ቤት አባሎች የየራሳቸውን የስራ ቋንቋ በህግ ይወሰናሉ” ይላል፡፡ በአንቀጽ 39/2/ ደግሞማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብና ህዝብ በቋንቋው የመናገር፣የመፃፍ፣ ቋንቋቸውን የማሳደግ እና ባህሉን የመግለጽ፣ የማዳበርና የማስፋፋት እንዲሁም ታሪኩን የመግለጽ መብት አለው ይላሉ፡፡
የባህል ፖሊሲያችን ለቋንቋዎቻችን ልማት የሠጠው ትኩረት፣
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግስት የባህል ፖሊሲ በተመሳሳይ መልኩ ከህግ መንግስታዊ ጽንስ ሀሳቦች መነሻ ተቀርጾ በ1990 ዓ/ም ፀድቆ ወደ ስራ ተገብቶ እየተሰራበት የነበረው እና በአሁኑ ወቅት የአለም አቀፍ እና የአገራችን የባህል ኢንዱስትሪዎች እድገት ተጨባጭ ሁኔታዎችን በመገንዘብ እንዲከለስ ተደርጓል፡፡ የባህል ፖሊሲው ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ለጋራና ለተናጥል እድገታቸው መሰረት የሆኑ የጋራ የባህል እሴቶቻቸውን ማጎልበት እንዲችሉ ዋስትና ሰጥቷል፡፡ ከዚህ ጋር በማያያዝ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ህዝቦች ቋንቋዎች እና ስነ - ቃሎች የልማት አቅጣጫ በርካታ ነገሮችን ያውሳል፡፡ በሰነዱ በተለያዩ አንቀጾች እንደተመለከተው በመላው አገሪቱ የሚገኙ ቋንቋዎች እና ቀበልኛዎች በስፍራና በደረጃ ተለይተው እንዲመዘገቡ ይደርጋል፤የብሄሮች፣ ብሄረሰቦች፣ ህዝቦች፣ ስነ - ቃሎች በሚነገሩበት ስፍራ ታሪካዊና ባህላዊ እሴታቸው የተጠበቀበት ሳይንሳዊ ምዝገባ ይደረግላቸዋል ይላል፡፡ እንዲሁም የሀገሪቱን ቋንቋዎች ስርጭት የሚያመለክት የቋንቋ ካርታ ይዘጋጃል፡፡ ፊደል ለሌላቸው ቋንቋዎች የተናጋሪው ህብረተሰብ ስነ ልቦናና አመለካከት የተገነዘበበት የፊደል ቀረፃ በማከናወን አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፤ ፊደል ያሏቸው ቋንቋዎች ያለባቸውን ችግር ለመፍታት በአፃፃፍ ስርአት ጥናት ላይ የተመረኮዘ ማሻሻያ ይደረግላቸዋል፤ በሀገሪቱ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦች፣ ህዝቦች ቋንቋዎች መዛግብተ ቃላትን፣ አውደ ጥበቦችንና የሰዋሰው መፃህፍትን በማዘጋጀት የህዝቦች ስነ ጽሁፋዊ ባህል የሚዳብርበት ሁኔታ ያመቻቻል ይላል፡፡
ብሔር ብሔረሰቦች በዓል በተለያየ ዝግጅት ሲከበር
የአፍ መፍቻ ቋንቋ ስንል አንድ ሰው በህፃንነቱ ከሁሉም በፊት የሚማረው እና አካባቢውን የሚረዳበት፣ የሚገልጽበትና የሚግባባበት የመጀመሪያ ቋንቋ ነው፡፡
በአፍ መፍቻ ቋንቋ የመናገር ጥቅሞች በጥቂቱ፤
· በህፃናት የቋንቋ እና የትምህርት እድገት ወሳኝ የሆነ
አወንታዊ ውጤት ያመጣል፣ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋ ሲማሩ የሚማሩት ቋንቋውን ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ትምህርቶች ጽንስ ሀሳቦችንና ክህሎቶችን የሚያሳድጉበት ነው፣የህፃናት የአፍ መፍቻ ቋንቋ እድገት ለተጨማሪ ቋንቋዎች እድገት አመልካች ነው፣ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም ያዳርሳል፣የህሊና ልማት በማምጣት ሙሉ ስብእናው የተገነባ በማንነቱ የሚኮራ ትውልድ ለመቅረጽ ያግዛል፣አካባቢውን የሚገነዘብ ሁኔታዎችንና ክስተቶችን በቀላሉ የሚረዳ ለለውጥ ዝግጁ የሆነ ዜጋን ማፍራት ይቻላል፡፡ ለእውቀት ሽግግር ንቁ እና ለፈጠራ ችሎታ ብቁ የሆነን ዜጋን ያበረክታል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችን በማሳደግ በባህላዊ ምርቶች ተጠቃሚነትን ያጠናክራል፡፡
በቋንቋው ተናጋሪ ህብረተሰብ አስተዳደርም ሆነ በተለያዩ ሙያዎች በስራ ቋንቋነት የማገልገል እድል ይፈጥራል፡፡ ይህን መሰረት በማድረግም የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የአዊኛ እንደ አፍ መፍቻ በማስተማር ደረጃ ያለበትን ሁኔታ በተማሪዎች፣በመምህራን እና በትምህርት ቤቶች በሚከተለው ሠንጠረዥ ለማሳየት እንሞክራለን፡፡
ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ሲማሩ
መደበኛ የመጀመሪያ ደረጃ በአፍ መፍቻ ቋንቋ
|
ዓመተ ምህረት
|
የተቋማት ብዛት
|
የመምህራን ብዛት
|
የተማሪ ብዛት
|
ሴክሽን
|
ጥምርታዎች
|
አዊኛ አንድ 1
የትም/ዓ/የሚሰጥ ተቋማት
|
|
ወ
|
ሴ
|
ድ
|
ወ
|
ሴ
|
ድ
|
|
|
|
|
|
1987
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
1988
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
|
1989
|
5
|
10
|
|
10
|
191
|
72
|
263
|
8
|
1፡26
|
1፡33
|
|
|
1990
|
65
|
109
|
11
|
120
|
5948
|
2605
|
8553
|
123
|
1፡71
|
1፡70
|
|
|
1991
|
70
|
138
|
29
|
167
|
11875
|
6741
|
18616
|
197
|
1፡111
|
1፡94
|
|
|
1992
|
72
|
189
|
106
|
295
|
16317
|
10388
|
26705
|
295
|
1፡91
|
1፡91
|
|
|
1993
|
72
|
199
|
133
|
332
|
20197
|
13494
|
33691
|
387
|
1፡101
|
1፡
|
|
|
1994
|
73
|
236
|
157
|
393
|
20387
|
13590
|
33977
|
390
|
1፡86
|
1፡
|
|
|
1995
|
76
|
402
|
224
|
626
|
21056
|
14437
|
35493
|
443
|
1፡57
|
1፡
|
|
|
1996
|
80
|
327
|
216
|
543
|
23094
|
17548
|
40642
|
541
|
1፡75
|
1፡
|
10
|
|
1997
|
96
|
526
|
358
|
884
|
30352
|
25461
|
55813
|
797
|
1፡63
|
1፡
|
60
|
|
1998
|
111
|
553
|
485
|
1038
|
35085
|
30620
|
65705
|
1009
|
1፡63
|
1፡
|
80
|
|
1999
|
135
|
767
|
477
|
1244
|
36795
|
33643
|
70438
|
1118
|
1፡57
|
1፡
|
102
|
|
2000
|
140
|
822
|
574
|
1396
|
43222
|
40146
|
83368
|
1420
|
1፡60
|
1፡
|
160
|
|
2001
|
167
|
1206
|
769
|
1975
|
46700
|
44429
|
91129
|
1593
|
1፡47
|
1፡
|
|
|
2002
|
189
|
1074
|
859
|
1933
|
45702
|
45257
|
90959
|
1652
|
1፡48
|
1፡
|
187
|
|
2003
|
210
|
1234
|
896
|
2130
|
50003
|
50559
|
100562
|
2014
|
1፡48
|
1፡
|
|
|
2004
|
227
|
1417
|
989
|
2406
|
46739
|
48293
|
95032
|
2121
|
1፡40
|
1፡45
|
|
|
2005
|
231
|
1703
|
1014
|
2717
|
47622
|
50858
|
98480
|
2029
|
1፡39
|
1፡49
|
|
|
2006
|
242
|
1746
|
1127
|
2873
|
52029
|
53572
|
105601
|
2243
|
1፡37
|
1፡47
|
|
|
2007
|
254
|
1770
|
1241
|
3011
|
55657
|
54732
|
110389
|
2405
|
1፡37
|
1፡45
|
|
|
2008
|
265
|
1826
|
1288
|
3114
|
59463
|
58907
|
118370
|
2600
|
1፡38
|
1፡46
|
|
ምንጭ ከአዊ ብሔ/አስተዳደር ትምህርት መምሪያ
ከላይ በሰንጠረዥ እንደተመለከተው በሁሉም ዘርፍ አሃዛዊ መረጃው እያደገ የመጣ ቢሆን ቋንቋውን ለማሳደግ እና ከነበረበት የአመለካከት ችግር ከማውጣት ግን መሰረታዊ ችግር ያለበት መሆኑን ልንገናዘብ ችለናል፡፡ስለሆነም ውድ አንባቢያን ልማታዊ መንግስታችን ለቋንቋዎች እድገት የሰጠውን ዕድል በመጠቀም ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ በተለይም በከተማ ህብረተሰብ አካባቢ ለቋንቋው ያለውን የአመለካከት ችግር እንዲሁም በአመራሩ፣በወላጁ፣በተማሪዎች እና በአጠቃላይ የማህበረሰብ ክፍል ላይ እየታየ ያለውን የትኩረት ማነስ እና የአመለካከት ችግር ለመቅረፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል፡፡